Discussion Quotes፡ Binyam TA Amanueal Zawdie ወንድማችን አማኑኤል፤ ፍርድ የለም ሳይሆን ፍርዱ ዘላለማዊ ሳይሆን በጊዜ የተገደበ ነው። እ/ር ፉጡራኑን በእሳት እየቀቀለ ለዘላለም የማሰቃየት አባዜ እየለብትም ፍርዱ ሲገለጥ በአላልማ ነው አላማውም ጽድቅን ለማስተማር ነው። ትንቢተ ኢሳይያስ 26፡9 #ፍርድህን በምድር ባደረግህ ጊዜ በዓለም የሚኖሩ #ጽድቅን #ይማራሉና ። ለምሳሌ ጌታ እየሱስ ስለ ተናገረው ድንቅ ምሳሌ ተደጋግሞ በተለያየ መልኩ በብዙ ወገኖች ፍቺው ቢነገርም የተነገረበትን መንፈስ ጋር የተላለፉ ብዙ ወገኖች ያሉ ይመስላል በትንሹ ቢረዳ ቀለል ባለ መልኩ ለማቅረብ እሞክራለሁ። የማቴዎስ ወንጌል 25-41 በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል፦ እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ።
(መተርጎም የነበረበት) የማቴዎስ ወንጌል 25-41 በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል፦ እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘመኑ እሳት ከእኔ ሂዱ። “ይሄ የእየሱስ ክርስቶስ ዲክሽነሪ ነው። ”
(Matt 25:41 [YLT])
Then shall he say also to those on the left hand, Go ye from me, the cursed, to the fire, the age-during, that hath been prepared for the Devil and his messengers;
(Matt 25:41 [Weymouth])
“Then will He say to those at His left, “‘Begone from me, with the curse resting upon you, into the Fire of the Ages, which has been prepared for the Devil and his angels.
በቀደም እንዳየነው የማቴዎስ ወንጌል 25/31 የሚያወራው ጌታን እንደ ግል አዳኝ አድርጎ ግለሰቡ መቀበሉ ወይም ስላለመቀበሉ የተነገረ አይደለም የሚያወራው ስለ አህዛብ መለየት ነው እነሱ ጌታ እየሱስን እንዴት እዳስተናገዱት ነው ያም ማለት ለጌታ ወንድሞች በጎ ያደረጉና ያላደረጉትን እየለየ ነው ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ወንድሞቼ ለአንዱ እንኳ ስላደረጋችሁት ለእኔ አደረጋችሁት ወደ ፍርድ የመጡት ጌታን ስላልተቀበሉ አይደለም ። ይህን ከደህንነት ጋር ምንም አያገናኘውም። “40 ንጉሡም መልሶ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ወንድሞቼ ለአንዱ እንኳ ስላደረጋችሁት ለእኔ አደረጋችሁት ይላቸዋል።” ከዚህ ከሚቀጥለው ቃላት ውስጥ ጌታን እንደግል አዳኝህ አልተቀበልክም የሚል አለ?የለም እርሱ ወንድሞች ብሎ ሊጠራ የማያፍርባቸውን አሁንም እንደሚታየው መልካምን ስራ ስላልሰሩና ስለሰሩ ህዝቦች እያወራ ነው። 34 ንጉሡም በቀኙ ያሉትን እንዲህ ይላቸዋል፦ እናንተ የአባቴ ቡሩካን፥ ኑ፤ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ። 35 ተርቤ አብልታችሁኛልና፥ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛልና፥ እንግዳ ሆኜ ተቀብላችሁኛልና፥ ታርዤ አልብሳችሁኛልና፥ 36 ታምሜ ጠይቃችሁኛልና፥ ታስሬ ወደ እኔ መጥታችኋልና። 37 ጻድቃንም መልሰው ይሉታል፦ ጌታ ሆይ፥ ተርበህ አይተን መቼ አበላንህስ? ወይስ ተጠምተህ አይተን መቼ አጠጣንህ? 38 እንግዳ ሆነህስ አይተን መቼ ተቀበልንህ? ወይስ ታርዘህ አይተን መቼ አለበስንህ? 39 ወይስ ታመህ ወይስ ታስረህ አይተን መቼ ወደ አንተ መጣን? 40 ንጉሡም መልሶ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ወንድሞቼ ለአንዱ እንኳ ስላደረጋችሁት ለእኔ አደረጋችሁት ይላቸዋል። 41 በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል፦ እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ። 42 ተርቤ አላበላችሁኝምና፥ ተጠምቼ አላጠጣችሁኝምና፥ እንግዳ ሆኜ አልተቀበላችሁኝምና፥ 43 ታርዤ አላለበሳችሁኝምና፥ ታምሜ ታስሬም አልጠየቃችሁኝምና። 44 እነርሱ ደግሞ ይመልሱና፦ ጌታ ሆይ፥ ተርበህ ወይስ ተጠምተህ ወይስ እንግዳ ሆነህ ወይስ ታርዘህ ወይስ ታመህ ወይስ ታስረህ መቼ አይተን አላገለገልንህም? ይሉታል። 45 ያን ጊዜ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ለአንዱ ስላላደረጋችሁት ለእኔ ደግሞ አላደረጋችሁትም ብሎ ይመልስላቸዋል።
የማቴዎስ ወንጌል 25-46 እነዚያም ወደ ዘላለም ቅጣት፥ ጻድቃን ግን ወደ ዘላለም ሕይወት ይሄዳሉ። በግሪኩ ዘላለም ቅጣት፥ “kolasin aionion.” Kolasin “punishment ቅጣት፤, chastening አሳዶ መቅጣት፤ , correction ማረም, to cut-off as in pruning a tree to bare more fruit መቁረጥ ልክ እንድን ዛፍ አብዝቶ እንዲያፈራ እንደ መግረዝ.” “aionions” የሚለው ቃል የተረጎመ ነው የቃሉ ስር ወይም፡ ንብረትነቱ “EION” ነው። ትርጉሙም “ዘመን age” ማለት ነው። ሁለቱ የተለያየ ትርጉም ያላቸው ናቸው ማለት አይደለም ። aion(the noun form) ሰዋሶው ወይም ነባር ስም ሲሆን aionions (the adjective form ቅጽል ነው። ሁለቱ ቃላት ሰዋሶው እና ቅፅል ናቸው። ለምሳሌ ሳምንት ሰዋሰው ሲሆን ሳምንታዊ ደግሞ ተቀፅላው ነው። ልክ እለት፦ እለታዊ, አመት ፦አመታዊ እንደሚባለው መለት ነው። Greek word “aion” (Strongs #165) or its adjective form “aionios” (#166).
እንግዲያው ይህን ካስተዋልን ተብሎ መተርጎም የነበረበት “የማቴዎስ ወንጌል 25-46 እነዚያም ወደ ዘመኑ ቅጣት፥ ጻድቃን ግን ወደ ዘመኑ ሕይወት ይሄዳሉ።” ወደ ዘመየኑ ቅጣቱና የጊዜው ጉዳይ ስናይ ወደ ቅጣት የሚሄዱትም ለዘላአለም ሊደመሰሱ ወይም ሊሰቃዩ ሳይሆን 1,ኛ”Kolasin “punishment ቅጣት፤(እንዲቀጡ), 2,ኛchastening አሳዶ መቅጣት፤(ይህ ቃል chasteneth በመጽሐፍ ቅዱስ መሰረት እንዴት እንደተጠቀመበት እናስተውል KJV Heb 12/6 For whom the Lord loveth he chasteneth, and scourgeth every son whom he receiveth) , 3,ኛcorrection ማረም (Correctional judgement የሚያርም ፍርድ ነው), 4,ኛto cut-off as in pruning a tree to bare more fruit መቁረጥ ልክ እንድን ዛፍ አብዝቶ እንዲያፈራ እንደ መግረዝ.”
ጻድቃን ግን ወደ ዘመኑ ሕይወት ይሄዳሉ። የእ/ር ህይወት በባህርዩ ዘልአለማዊ ቢሆንም ያ ህይወት የተወጋው ዘልአለማዊ ባልሆነ ማንነት ላይ ስለሆነ የዘመኑ ህይወት ተባለ ።
(Matt 25:46 [YLT])And these shall go away to punishment age-during, but the righteous to life age-during.’ ወንድም ቢንያም ።