
የሐዋርያው ጳውሎስ እና የሐዋርያው ያዕቆብ መልእክት ይጋጫሉን?
by Brother Binyam T. Alemayehu 1/12/2018
‘ነገር ግን አንድ ሰው “አንተ እምነት አለህ፤ እኔ ሥራ አለኝ” ይላል። እምነትህን ከሥራ ለይተህ አሳየኝ፤ እኔም እምነቴን በሥራዬ አሳይሃለሁ። ‘ያዕቆብ 2:18
ያዕቆብ 2:18 የአንድ ተግባራዊ ግልጦት የውስጥ ስሜት ነፀብራቆች ናቸው። የእርስዎ እርምጃዎች ከልብዎ ስውር ሃሳብ የተዘጋጁ ፍሬዎች ናቸው። በእውነት እግዚአብሔር መንፈሳዊውን ግዛት ለማስተዋል ለመስማት ለማየት ዓይን እና ጆሮ ሰጥቶን ከሆነ ያ በእርስዎ ድርጊት ውስጥ ግልጽ ይሆናል በፍሬዎም ይታያል። ምክንያቱም “1, * መስማት” እና “2, * መታዘዝን” ስናስተውል ከዕብራይስጥ ቃል * ሽማዕ shema የመጡ ተመሳሳይ ወይም መንታ ትርጉም ከያዘ ቃል የተገኙ ናቸው፡ የአንድ ቃል ሁለት ፍቺ ናቸው። ከእግዚአብሔር በእውነት የሚሰማ ጆሮ የተሰጦት ከሆነ ያለጥርጥር ከዚያ ቡሃላ ድምፁን መስማታችሁ በመታዘዛችሁም ውስጥ ይንጸባረቃሉ። አምላክ ድል ነሺ overcomer ልትሆኑ የጠራችሁ ከሆነ፡ በድል ነሺ ተግባራዊ ህይወት ይመላለሱ ይገለጡ። አንድ ድል ነሺ overcomer ነኝ ብሎ ሚናገር ሰው አይደለም ነገር ግን ድርጊቶቹ ለአንድን ሰው ስያሜውን ያመጡታል። ያዕቆብ 2:18 የእሱን ቃላት መርህ ነው ያንጸባረቀው።
ድል ነሺ እኮ በቀላሉ በማስተዋሉ ፈጣን የሆነ መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን መንፈሳዊ ጆሮ ያለው ና የስማ ሰምቶም የታዘዘ ነው።
የዮሐንስ ራእይ
2፥7 መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ። ድል ለነሣው በእግዚአብሔር ገነት ካለው ከሕይወት ዛፍ እንዲበላ እሰጠዋለሁ።
2፥11 መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ። ድል የነሣው በሁለተኛው ሞት አይጐዳም።
2፥17 መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ። ድል ለነሣው ከተሰወረ መና እሰጠዋለሁ፥ ነጭ ድንጋይንም እሰጠዋለሁ፥ በድንጋዩም ላይ ከተቀበለው በቀር አንድ ስንኳ የሚያውቀው የሌለ አዲስ ስም ተጽፎአል።
2፥29 መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ።
3፥6 መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ።
ጌታ ሰዎች ሁሉ ላይ የበረከት መልእክት አስተላልፏል በረከቱም “1, * ለሚሰሙና” በተግባር 2 * ለሚታዘዙለት) ሁሉ ላይ ነው። በዕብራይስጥ ቋንቋ ውስጥ, idiom ቃል ይህ የዕብራይስጥ ፈሊጥ ነው። በዕብራይስጥ ቋንቋ ውስጥ, shemameans የቃሉ ፍቺ ድርብ ነው መስማት እና መታዘዝ ነው።
ዘዳግም 6.4 ስማ [* ሽማዕ] እስራኤል ሆይ! ጌታ አምላካችን ነው, አንድ ጌታ ነው! የቃሉ ትእዛዝ የሚጀምረው ስማ/ታዘዝ በማለት ነው።
አንድ ሰው እንግዲህ የሉኡሉን ቃል ሰምቶ የማይታዘዝ ከሆነ ታዲያ እንዴት ብሎ ቃሉን ሰምተዋል ሊባል ይችላል? አንድ ሰው ደግሞ ካልታዘዘ በስተቀር በዕብራይስጥ ፈሊጥ ውስጥ ማንም ገና ሰውየው በእውነት አልሰማም። ይህ ጽንሰ-ሐሳብ ደግሞ ለያዕቆብ ‘ትምህርት መሠረት ነው። እሱም * በያዕቆብ 1:22 ላይ እንዲህ ይላል * 22 ‘ቃሉ የሚናገረውን አድርጉ እንጂ ሰሚዎች ብቻ ሆናችሁ ራሳችሁን አታታልሉ። ‘
እምነት ከመስማት ነው መስማትም ከእግዚአብሔር ድምጽ ወይም ቃል ነው። እናም እግዚአብሔርን መስማትህ የተረጋገጠ የሚሆነው ሰምተህ ከታዘዝክ ነው። ነብዩ ዮናስ እስኪ ሰማ እስከ ሲኦል መውረድ ነበረበት። አንዳድ ሰው በመገለጥ ስለማይሰማ መንፈስ ቅዱስ ወደ ተግባር ትምህርት ቤት ያስገባውና በተግሳጽ ጆሮውን የከፈተዋል። “ትንቢተ ዮናስ 2/3 በመከራዬ ሳለሁ ወደ አምላኬ ወደ እግዚአብሔር ጮኽሁ፥ እርሱም ሰማኝ፤ በሲኦልም ሆድ ውስጥ ሆኜ ጮኽሁ፥ ቃሌንም አዳመጥህ።”
አንድ ሰው በእብራዊን ቋንቋ የጌታን ድምጽ ሰማሁ ካለ ፈጽሞ ሰምቶ ፈጽሞ መታዘዙን የሚያሳይ ነው። ሰምቶ ካልታዘዘም ፈጽሞ አልሰማም። በመገለጥ እንዲሰማም በሌላ በተግባር ሂደት ያልፋል። “በመከራ ጆራቸውን ይከፍታል። እዮብ36፡15 በእብራይስጥ መከራ የሚለው ውጥረት ይለዋል። አንዳንድ ጊዜ ለምን ይሄ ሁሉ ውጥረት በመንገዳችን እንደ ሚያልፍ እንደነቃለን። እንደ ዛም ሆኖ ነገር ሁሉ ተያይዘው ለበጎ እንዲደረግ እንረዳለን። በብዙ መከራ ማለፋችንም ለብዙ አላማ እንደሆነ እናውቃለን። ከዛ ውስጥ አንዱ ጆራችን እዲከፈት ነው። ጳውሎስ የደቀ መዛምርቱን ልብ በማበረታታትና በእምነታቸወ ጸንተው እንዲሩ በመምከር “ወደ እ/ር መንግስት ለመግባት በብዙ መከራ (ግሪክ፦ pressure, እንደ አገባቡ ቃሉ ሲተረጎም ውጥረት ግፊት መገፋፋት ተጽኧኖ የሚያመጣ ውጥረት )ማለፍ አለብን “” ሐዋ14፡22 ይህም ውጥረት ከአሮጌው አውጥቶ ወደ አዲሱ ተጭኖ ያስገባናል። እ/ር አምላክ ጥበበኛ ነው። አንዱን ውጥረት ከአንድ ነገር ለማውጣትና በተመሳሳይ ሰአትም የስጋን ፈቃድ ሰብሮ የመንፈስን ድምጽ ወደ መስማት ግዛት ያመጣናል።” ከስጋ ድካምም ወደ መንፈስ ብርታት ዘወር እንላለን።
እንደተነጋገር ነው እምነት ከመስማት ነው መስማትም ከእግዚአብሔር ድምጽ ወይም ቃል ነው። እናም እግዚአብሔር መስማትህ የተረጋገጠ የሚሆነው ሰምተህ ከታዘዝክ ነው። በዚህም መሰረት ያዕቆብን እንስማው እስቲ
‘ነገር ግን አንድ ሰው “አንተ እምነት አለህ፤ እኔ ሥራ አለኝ” ይላል። እምነትህን ከሥራ ለይተህ አሳየኝ፤ እኔም እምነቴን በሥራዬ አሳይሃለሁ። ‘ያዕቆብ 2:18
* የጳውሎስ እና ያዕቆብ መልክቶች በተመለከተ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ አንዳንድ ውዝግቦች አሉ። ማስተዋል ያለብን ጳውሎስ እኛ በሥራ ሳይሆን በእምነት የጸደቅን መሆናቸውን ለማሳየት የአብርሃም ምሳሌ ተጠቅማል ።
ሮሜ.4:1-4 *. ያዕቆብ እምነታችንን በሥራ የሚረጋገጥ መሆኑን ለማሳየት የአብርሃም ተመሳሳይ ሰው ምሳሌ ይጠቀማል። አንዳንዶች ጳውሎስና ያዕቆብ እርስ በርሳቸው እንደ ሚጋጩ ይናገራሉ ብሎም አንዳንድ ክርስቲያኖች ከአንዱ ለመወገን ጎራ ይለያሉ ።
* ያዕቆብ 2.21-24 ሌሎች ደግሞ ጳውሎስ በእምነት ብቻ ለጸደቁ ሰዎች አይሁዳውያን ላልሆኑ ነው መልክቱ ሲሉ
ሌሎቹ ደግሞ ያዕቆብ በጻፈው ደብዳቤ በሆነ መንገድ በሥራ ለጸደቁ የአይሁድ ሰዎች መጻፉ ነበር ይላሉ።
* የጌታ ቃል ሲነግረን እምነት በፍቅር የሚሰራ ነው ይለናል። እምነት ፍቅር ከሌለው እግር የሌለው ሽባ ይሆናል እምነትን የሚያሰራው፡ሃይል ፍቅር ነው። ፍቅር ታዛዥ ነው። እምነት መስራቱ በሥራ የተረጋገጠ መሆን ይኖርበታል እምነት ዱዳ አይደለም ይናገራል “አመንኩ ስለዚህም ተናገርኩ”። በእብራዊያን 11 ያሉ የእምነት ግዙፎችን አስተውሉሁሉ እምነታቸውን በስራ ገልጠዋል።
‘አቤል ከቃየል ይልቅ የበለጠ መሥዋዕት ለእግዚአብሔር በእምነት አቀረበ። እግዚአብሔር ስለ ስጦታው በተናገረለት ጊዜ፣ እርሱ በእምነት ጻድቅ እንደሆነ ተመሰከረለት፤ ቢሞትም እንኳ እስከ አሁን በእምነቱ ይናገራል። ‘ዕብራውያን 11:4
‘ሄኖክ ሞትን እንዳያይ ከዚህ ዓለም በእምነት ተወሰደ፤ እግዚአብሔርም ስለ ወሰደው አልተገኘም፤ ከመወሰዱም በፊት እግዚአብሔርን ደስ እንዳሰኘ ተመስክሮለታልና። ደግሞም ያለ እምነት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ምክንያቱም ወደ እግዚአብሔር የሚቀርብ ሁሉ እግዚአብሔር መኖሩንና ከልብ ለሚሹትም ዋጋ እንደሚሰጥ ማመን አለበት። ‘ ዕብራውያን 11:4-5
‘ኖኅ ገና ስለማይታየው ነገር እግዚአብሔር ባስጠነቀቀው ጊዜ፣ እግዚአብሔርን ፈርቶ ቤተ ሰዎቹን ለማዳን መርከብን በእምነት ሠራ፤ በእምነቱ ዓለምን ኰነነ፤ በእምነትም የሚገኘውን ጽድቅ ወራሽ ሆነ። ‘ ዕብራውያን 11:7
‘አብርሃም ርስት አድርጎ ወደሚቀበለው ስፍራ እንዲሄድ በተጠራ ጊዜ በእምነት ታዘዘ፤ ወዴት እንደሚሄድ ባያውቅም፣ እሺ ብሎ ሄደ። በባዕድ አገር እንዳለ መጻተኛ በተስፋዪቱ ምድር በእምነት ተቀመጠ፤ የተስፋውን ቃል አብረውት እንደሚወርሱት እንደ ይስሐቅና እንደ ያዕቆብ በድንኳን ኖረ፤ ምክንያቱም መሠረት ያላትን፣ እግዚአብሔር የሠራትንና የፈጠራትን ከተማ ይጠባበቅ ነበር። አብርሃም ምንም እንኳ ዕድሜው ቢገፋም፣ ሣራም #11፥11 ወይም ሣራ … አብርሃምም … ስለቈጠረች ሦስት ወር ሸሸጉት፤ የንጉሡንም ዐዋጅ አልፈሩም። ራሷ መካን ብትሆንም፣ ተስፋን የሰጠውን ታማኝ አድርጎ ስለ ቈጠረ #11፥11 ወይም ሣራ … አብርሃምም … ስለቈጠረች ሦስት ወር ሸሸጉት፤ የንጉሡንም ዐዋጅ አልፈሩም። በእምነት የልጅ አባት ለመሆን በቃ። ስለዚህ እንደ ሞተ ሰው ከሚቈጠር ከዚህ ከአንድ ሰው፣ እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛና እንደ ባሕር ዳር አሸዋ ተቈጥሮ የማያልቅ ዘር ተገኘ። ‘ዕብራውያን 11:8-12
እናም ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ነው የያቆብ ነጥብ ። ማጠቃለያ እምነት የሚረጋገጠው በታዛዥነት ነው። ታዛዥነት ከሌለ ምንም መስማት የለም እና መስማት ከሌለ ምንም ዓይነት እውነተኛ እምነት የለም። ጳውሎስ * ሮሜ:14.23 ላይ እንዲህ ይላል ‘ በእምነት ያልተደረገ ሁሉ ኀጢአት ነውና።”
by Brother Binyam T. Alemayehu 1/12/2018