ወንድማችን ግሩም ማሞ ባነሳው ወቅታዊ ሃሳብ ላይ ከጨመርኩት የተጠቀሰ። Binyam TA 💯% እውነት ነው ሁሉንም ለመፈረጅ ጠቅልሎ በአንድ የሚያይ አይን ታማሚ ነው። አንድ ግዜ ያነበብኩት የጋቭሮቮች የባህርይ ቆንቋኖች ከመስገብገባቸው ብዛት ለቤት እንሳዎቻቸው የከረመ ድርቆሽ ሳር ካልሆነ ለምለም አረንጋዴ ሳር ስለሚወደድ አይሰጥዋቸውም። ለከብቶቻቸውና ለፈረሶቻቸው በልካቸው የተሰራ አረንጓዴ መነፅር ግጥም አድርገው ያሱሩላቸውና የከረመውን ሆነ ያገኙትን ለምለም አረንጓዴ ሳር ነው ብለው ግጥም አድርገው ያመነዥኩታል። ይህ ትውልድም የእይታው ሚዛን ይስተካከል ዘንድ የባእድ የባህል ወረራ ተጠቂ መሆን ለማቖም የዘረኝነት፣ የጎሰኝነት፣ መነፀር ማውለቅ ይገባዋል። በሚዛን የሚበድል በእግዚአብሔር ፊት ፀያፍ ነውና ጥሉ ከእግዚአብሔር ጋር እንጂ ከሰው ጋር አይደለም። ሰዋችን በዘር ሳይሆን በባህርያቸው ነው መፍረድ ያለብን። ክፉም በጎም ለራሱ ነው እግዚአብሔር ሁሉንም እንደስራው ያስረክበዋል። ጌታ እየሱስ የነገሮችን እውነተኛ ተፈጥሮ ስለሚረዳ አይኑ እንደሚያሳይ ጆሮው እንደሚሰማ አይበይንም። ልጅነት እንዲህ ነው። እግዚአብሔር የወደውን ልንወድ እግዚአብሔር የሚጠላውን ልንጠላ የግድ ነው። እግዚአብሔር ሰውን መውደድ ተገልጠዋል። ሀጥያትን ይጠላል። ሰውን ሁሉ በክርስቶስ ልንወድ ይገባናል። ከእግዚአብሔር ሃሳብ ጋር መስማማት መልካም ነው። እውነት ነው እግዚአብሔር ፍቅር ነው ፍቅሩን ካሰቃያቹሁት ግን በእውነት አምላካችን የሚባል እሳት ነው። በጥበብ የተሞላችው አያቴ ትዝ አለችኝ። እንዲህ ትል ነበር። “እግዜርን የጠላ ተሸክመው ያመጡታል ንጉስን የጠላ አስረው ያመጡታል” ሌላ ተመሳሳይ “እግዚአብሔር ሲቆጣ አይማታም በብትር ምክር እያሳሳተ ያደርጋል ድንብርብር” እስራኤሎችን ቅዱስን መንፈስ ስላስመረሩት ተቆጥቶ ያንን አንገተ ደንዳና ህዝብ በምድረ በዳ #እግዚአብሔር እራሱ #አሳታቸው የኮሪብንም ተራራ 40 አመት ዞሩ ዘመናቸውንም አስረጀ። ከእግዚአብሔር ጋር በነገር ሁሉ መስማማት መልካም ነው። ፀባዮ ነው እንበል ።ፀባያችን ክርስቶስ ነው። ህይወታችን የሆነው የክርስቶስ ባህርይ ይገለጥብን። ፍቅር ና ሰላም ይሁን ወንድም ቢኒ።