
የአለም መሰረት ሳይጣል ልጆች ነበሩ? መልሱ መንፈሳዊውን ነገር እንደ ማየት አቅማችን ይወሰናል። ልጅነት አለም ሳይፈጠር በፊት በመንፈሳዊው አለም በክርስቶስ ውስጥ ከሁላችን ጋር የነበረ ክብር ነው።
መጽሐፈ ኢዮብ 38: 4 ምድርን በመሠረትሁ ጊዜ አንተ ወዴት ነበርህ? ታስተውል እንደ ሆንህ ተናገር።5 ብታውቅስ መሠፈሪያዋን የወሰነ፥ በላይዋስ የመለኪያ ገመድ የዘረጋ ማን ነው? 6-7 አጥቢያ ኮከቦች በአንድነት ሲዘምሩ፥ የእግዚአብሔርም ልጆች ሁሉ እልል ሲሉ፥መሠረቶችዋን በምን ላይ ተተክለው ነበር?የማዕዘንዋንስ ድንጋይ ያቆመ ማን ነው?
1ኛ, *በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን ባቻ ሳይሆን መተርጎም ያለበት በክርስቶስ ኢየሱስ “ውስጥ” ተፈጠርን ነው።[created in(within) Christ Jesus ]
‘ምክንያቱም፣ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀልንን መልካም ሥራ እንድንሠራ በክርስቶስ ኢየሱስ “ውስጥ” የተፈጠርን [created in(within) Christ Jesus ]የእግዚአብሔር ፍጥረቱ ነን። ‘ኤፌሶን 2:10
ፍጥረቱ ሁሉ በእዛ ክብር ውስጥ ነበሩ። ከማይታየው የሚታየውን ፈጠረ ሲል የማይታየው እራሱ እግዚአብሔር ነው ከማንነት ወስዶ የሚታየውን ሰራ። ሁሉ ከሱ ወጥተዋልና ምንም እንካ እንደሁላችን በክርስቶስ ውስጥ ቢፈጠሩም እግዚአብሔር ወደሚታየው አካላዊ አለም ሲያመጣን
እንደወደደው ፍጥረትን ሁሉ ለከንቱነት አስገዝቶ ከእግዚአብሔር ክብር ከክርስቶስ አጉድሎ እንደገና ወደ ቀድሞው ክብራቸው እንደገና በክርስቶስ ሁሉን እየመለሰ ነው።
“የሰዎችን ልጆች ወደ አሳር አውረድካቸው የሰው ልጆች ሆይ ተመለሱ ትላለህ”
ልጆች ከሆንን ወራሾች ደግሞ ነን፤ ማለት የእግዚአብሔር ህይወት ወራሾች ነን፥ እስከ እግዚአብሔር ሙልአት የመድረስልችን ምስጢር ለእኛ ሳይሆን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ፍጥረትን ከከንቱነት ወደ ልጅነት ክብር አንድ ለማድረግ ለማዋሀድ ነው። በዚህ ህይወት በሙልአት እንወረስ ዘንድ
ፍጥረት በሙልአት ባያስተውለውም በናፍቆት ኅይል የእግዚአብሔር ልጆችን በክብር መከሰትን ለነፃነቱ ሲል ይራባል።
ልጆች ቀድሞ ወደ ጎደለባቸው የእግዚአብሔር ክብር ወደ ራሳቸው የክርስቶስ አእምሮ እንዲነጠቁና በክርስቶስ የተሰወረውን የእውቀትና የጥበብ መዝገብ ለፍጥረት ጥቅም እንዲበዘብዙ ከዙፋኑ ማለትም ከስልጣኑ ፊት ከሚፈሱልን
በሰባቱም የእግዚአብሔር መንፈስ ሙልአት በእግዚአብሔር መንፈስ፥ በጥበብ መንፈስ ፤ በማስተዋል መንፈስ፥ በምክር መንፈስ፤ በኃይል መንፈስ፥ በእውቀት መንፈስ፤ እግዚአብሔርን በመፍራት መንፈስ መገለጣችንን በናፍቆት ይጠባበቃል።
ፍጥረት ለከንቱነት ተገዝቶአልና፥ በተስፋ እግዚአብሔር ስላስገዛው ነው እንጂ በራሱ ፈቃድ ወዶ አይደለም፤ እግዚአብሔር ሁሉን ይምር ዘንድ ሁሉን ለእግዚአብሔር ባለመታዘዝ ሚስጥር ዘግቶታልና።
አሁን ተስፋው ፍጥረት ራሱ ከጥፋት ባርነት ነፃ ወጥቶ ለእግዚአብሔር ልጆች ወደሚሆን ክብር ነፃነት እንዲደርስ ነው። ለዚህም ፍጥረት ሁሉ እስከ አሁን ድረስ አብሮ በመቃተትና በምጥ መኖሩን እናውቃለንና።
እርሱም ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን የመንፈስ በኵራት ያለን ራሳችን ደግሞ የሰውነታችን ቤዛ የሆነውን በልጅነት ክብር በሙልአት እንወረስ ዘንድ እየተጠባበቅን ራሳችን በውስጣችን እንቃትታለን። ወንድም ቢኒ።