
መጽሐፍትንና የእግዚአብሔርን ኅይል ካወቅን አንስትም!
የማርቆስ ወንጌል 12/24 ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፦ መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ስለዚህ የምትስቱ አይደለምን? ”ቅዱሳን መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና“ ጌታ እየሱስ ለሰዱቃዊያንና ስተታተቸውን፡አሳይቶ እውነትን ለመመስረት የተጠቀመበትን ቃል እናስተውላለን። እነዚህ ሰዎች መጽሓፍትን እንደ ሚያነቡ የታወቀ ነው። በብዙ ቦታ ላይ የቃሉን ፊደል ይጠቅሳሉና።
ነገር ግን የቃሉን ትክክለኛ ጠአምና አመልካች መንፈሳዊ ትርጉማቸውን ግን እ/ር እንደ ሚመለከተው አያስተውሉትም አያውቁትም። ደግምም በቃሉ ፍቺ ላይ የሃሰት ግንባታን ይገነባሉ ያስቀምጣሉና። ሌላው ደግሞ የእግዚአብሔርን ኃይል ያለማወቅ ለስህተታቸው ሌላኛው ምክንያት እንደሆነ ይናገራል። ህይወትን የሚሰጥ መንፈስ ነው ቃሉ ደግሞም ከመንፈስ ሲነገር ህይወትና መንፈስ ነው። ከስጋዊ አይምሮ ሲነገር ግን ፊደል ነው። ፊደል ደግሞ ይገድላል። ስጋዊ አእምሮ ማለት ሞት ነውና በአንፃሩ መንፈሳዊ አእምሮ ማለት ህይወትና ሰላም ነው። “Rom 8/6 For to be carnally minded is death; but to be spiritually minded is life and peace.”KJV
ይህን የJMT ትርጉም አስተውሉ “Rom 8/6. For the thinking (mind-set; way of thinking; disposition; understanding and inclination; the minding; the opinion; the thought) of the flesh [is] death, yet the thinking (mind-set; disposition; thought and way of thinking) of the spirit (or: the Spirit) [is] Life and Peace,”
መዝሙረ ዳዊት 62 /11 እግዚአብሔር አንድ ጊዜ ተናገረ፥ እኔም ይህን ብቻ ሰማሁ ኃይል የእግዚአብሔር ነው፥
Ps 62/11 God hath spoken once; twice have I heard this; that power belongeth unto God
መጽሐፈ ዜና መዋዕል ቀዳማዊ 29/11 አቤቱ፥ በሰማይና በምድር ያለው ሁሉ የአንተ ነውና ታላቅነትና ኃይል፥ ክብርም፥ ድልና ግርማ ለአንተ ነው አቤቱ፥ መንግሥት የአንተ ነው፥ አንተም በሁሉ ላይ ከፍ ከፍ ያልህ ራስ ነህ።
1Chr 29/11 Thine, O Lord, is the greatness, and the power, and the glory, and the victory, and the majesty: for all that is in the heaven and in the earth is thine; thine is the kingdom, O Lord, and thou art exalted as head above all.
ትንቢተ ዳንኤል 2/20 ዳንኤልም ተናገረእንዲህም አለ፦ ጥበብና ኃይል ለእርሱ ነውና የእግዚአብሔር ስም ከዘላለም እስከ ዘላለም ይባረክ
Dan 2/20 Daniel answered and said, Blessed be the name of God for ever and ever: for wisdom and might are his:
እግዚአብሔር ልናስተውለው ከምንችለው በላይ በኅይሉ ወሰን የለውም። ነገር ግን የማይወሰነውን የእስራኤልን ቅዱስ በውስንየዋ የሰው አይምሯቸው ታላቅ ኅይሉ ወስነውታል። ይህም እንዲስቱ ምክንያት ሆናቸዋል። የእግዚአብሔር ኅይሉ ግን በየዘመናቱ ወሰን የሌለው ታላቅ ሆኖ ለስጋ ለባሽ ታይተዋል። ለፃድቅ ሃብቱ ትጋቱ ነውና ማንበብ ውስጥ ሃይል አለ ማንበብ ጥሩነው። ከዛ በላይ ግን እ/ር አባት አእምሮአቸውን እንዲ ከፍትልን መፀለይ መልካም ነው። “አትጠይቁምና አትቀበሉም። እየሱስ” አእምሮን የሚከፍት አንድ አለ። “የሉቃስ ወንጌል 24/45 በዚያን ጊዜም መጻሕፍትን ያስተውሉ ዘንድ አእምሮአቸውን ከፈተላቸው፤” አሜን።
በወንድም ቢንያም አለማየሁ