ከውይይት የተጠቀሰ፤ አየህ ወንድሜ ብራዘር በሌ፤ ከአረጀ አቁማዳ መናኛውን ወይን መቅዳት ቀላል እንደሆነ አንደቀደክው እኮ። አስቀድመህ መልካሙን የወይን ጠጅ ክርስቶስን አጠጥተህ ካሰከርከን በኋላ መናኛውን ብታቀርብ ጥሩ ነበር።በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም ስለዚህ የቀዳከውን ተመልከት፤ የማስታረቅ ቃል በአንተ ያኖረው የታመነ ነው። አዲሱን የወይን ጠጅ በአዲስ አቁማዳ ቅዳው፥ በክርስቶስ ሁለቱም ይጠባበቃሉ። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በአዲሱ ወይን እና በአሮጌ ወይን መካከል ያለው ልዩነት ምንድን ነው? መልሱን ድረስበ። የተሰወረውን ህይወትን አዲስን ቅኔ የሚዘምረውን አንድ የሆንክበትን ክርስቶስን በአንተ አሳያኝ ደግሞም ሰውን ሁሉ በዚያ ስታይ አሳየኝ አከብርሃለሁም። የምን እርቅ ነው? አትበለኝ የክርስቶስ አእምሮ የጥልን ግድግዳ የሚያፈርስ ነው የሚያስታርቅም ነው። ይህ ምን አይነት አቅም ነው ጎንህን እየወጉህ አባት ሆይ፥ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው ማለት?። አባት ይህን አቅም አያሳጣን። አሁን ያለው አካሄድ ጌታ ሆይ፥ ኤልያስ ደግሞ እንዳደረገ እሳት ከሰማይ ወርዶ ያጥፋቸው እንል ዘንድ ትወዳለህን? የሚል የክርስቶስ ደቀ መዝዝሙር የበዛበት ነው። ፍርድን የሚያዝ ጉደኛ ትውልድ ክርስቶስ ግን አይስማማም አጥፋ አጥፋ የሚለውን መንፈስ ይለየዋል ለይም ይልሃል። የሉቃስ ወንጌል 9፡55ኢየሱስ ግን ዘወር ብሎ ገሠጻቸውና “እናንተ ከምን ዐይነት መንፈስ እንደሆናችሁ አታውቁም፤ የሰው ልጅ የመጣው የሰውን ሕይወት ለማዳን ነው እንጂ ለማጥፋት አይደለምና” አላቸው፤ መካሪውንም ተመካሪውን ሰይፍ የሚያነሡ ሁሉ በሰይፍ ይጠፋሉና ሰይፍህን ወደ ሰገባው መልስ በለው። የእ/ር ሃሳብ ሲናገርና ሰው ሲናገር ሁላችንም እናውቀዋለን። ይገርማል እውነተኛ ተጽኖ እያአንዳንዳችን ሲነካን ደረጃው ይለያይ እንጂ መሃሪዎች ለመሆን ያለው የውስጥ ጦርነትና ፍልሚያ መታገላችን በሁላችንም ዘንድ መታየቱ ግልጽ ነው። ስለ ፍርድ ካለን ግንዛቤ የተነሳ ፍርድን እናዛለንና። በቀላሉ ሁላችንም “በተማራቹበት ምህረት መጠን መሃሪዎች ሁኑ” ተብሎ እንደ ተፃፈ በቀላሉ በተማርንበት ምህረት መሃሪዎች ሆነን ለፍጥረት መገለጥ ሲገባን ማለት ነው። ነብዩ ዮናስ የጌታን ቃል ተቀበለ እውነተኛ ነብይ ነበር። “የጌታን ቃል” መቀበል ድንቅ ነገር ነው። ያ ግን በራሱ በምህረት የተሞላን መሆናችንን አያሳይም። ዛሬ በዚህ መልኩ ገና በብዙ የሚቀረው ያልተሰራው ማንነታችን እንዲታይ እ/ር አንጫችቶን ይታዋል። ጥሩ ነው ይህም ባህሪ ከተሰወረበት ከሁላችን መገለጡ ለመጥፋቱ ነው ለክርስቶስ ቦታ ይለቃል። እውነቱ አንዳንድ ወንድሞች ፍርድን እንደጮሁት አይደለም የእ/ር አካሄድ ይለያል በሰው ልብ ብዙ አሳብ መኖሩ ብቻ ሳይሆን በሰው አንደበትም ፍሬ ከይሲ ብዙ ሙዋርት ይነገራል የፈለከውን መሬት ላይ ተንከባለክ ብትራገም የእግዚአብሔር ምክር ብቻ ግን እርሱ ይጸናል። ሰውን አንተና እኔ ስላጣን ላይ ውጣ ውረድ ስላልከው አይወጣም አይወርድምም እሱ የእ/ር ድርሻው ነው። ፍርድ ባዘዘ አይደለም ነገሩ አትድከሙ። እንደዛ ቢሆን ኖሮ ከወያኔ የባሰ ደርግ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ንጹሃን በቀይ ሽብር የፈጀ እና ፖለቲከኞችን ወጣቶችን የእርጉዝ ሆድ ሳይቀር በወታደር ሳንጃ እየቀደደ ነገ ወያኔና ተገንጣይ ሻብያ ትሆናለክ ወዘተ እያለ ግፍ ሰርቶ ምንም ያክል ነፍጥ አንስተው ቢዋጉት ስራቱን ቢገረሡት እ/ር ኮነሬል መንጌን በመልካም ሽምግልና እድሜውን እንዲጨርስ ፈቅዶሎታል ለአስተዋይ አእምሮ ይህ የሚነግረን የእ/ር ፍርዱ ምን እደሚሆን የሚያውቅ እርሱ ብቻ መሆኑን ነው። እውነትም ሰማይ ከምድር ከፍ እንደሚል፥ እንዲሁ መንገዴ ከመንገዳችሁ አሳቤም ከአሳባችሁ ከፍ ያለ ነው። ማለቱ እውነት ነው። እ/ር ለመሪያችን የእርቅንና የሰላምን መንፈስ ይስጠው ሁሉን የሚያቅፍበትን ጸጋ ያብዛለት ከክፉ ምክር ይሰውረው ለዘመኑ የተገባ የሚያስተዳድርበት ጥበብና የጽድቅ መንፈስ አይሰውርበት። ምሕረትና እውነት ተገናኙ፤ ጽድቅና ሰላም ተስማሙ።አሜን። ወንድም ቢኒ።