ለፈገግታ 2
አንድ አገልጋይ የመኪና ማቆሚያ ፈልጎ አጣ:: በዚህም ትልቅ ከተማ እየተጣደፈ ቀጠሮው ደርሶበት ማቆም ክልክል ነው በሚል ቀይ ቀጠና አቆመና በመኪናው መስተዋት እንዲህ የሚል ወረቀት ለጠፈ::<< ማቆሚያ ለማግኘት የህን የመኪና ማቆሚያ 10 ጊዜ ተሽከርክሬ ስለ አጣሁ ቀጠሮየም ሊያልፍብኝ ስለሆነ ያልተገባኝ ቦታ አቁሚያለሁ::<መተላለፋችንን ይቅር በል> >>የሚል ጥቅስ ጨምሮ ተወ
ሲመለስም ፖሊሱ እንዲህ የሚል ማስታወሻ ትቶለት አገኘ::ማስታወሻውም<< የህን የመኪና ማቆሚያ ለ10 አመት ተሽከርክሪያለሁ ትኬት ካልሰጠሁህ ስራየን አጣለሁ::<ወደ ፈተና አታግባን> የሚል ጥቅስ ጨምሮ ተወለት::
2 አንድ ጸሎት ከጸለየ ብዙ ጊዜ የሆነው ሰው ሊያገባ ጊዜው ሲደርስ የእዚያብሄርን ድምጽ በጥብቅ ይሻ ጀመረ:: እ/ር መልካም ነውና ደግሞም ይናገራልና በድምጹ ተገለጠለት: ሰውየውም ጥያቄውን ጠያይቆ ከተመለሰለት ቡሃላ በአንድ ጥያቄ አልተመለሰም ጌታ ሆይ አንድ ሺ አመት ለአንተ ምን ማለት ነው? ብሎ ቀጠለ ጌታም እንደ አንድ ቀን ነው እንዳውም እንደ አንድ ሰከንድ ነው ልጄ አለው:: ሰውየውም ቀጠለ አንድ ሚሊዮን ዶላር ለአንተ ስንት ነው ጌታ ሆይ? ጌታም መለሰ እንደ አንድ ሳንቲም ነው እንዳውም ምንም እንደማለት ነው: ልጄ አለው ሰውየውም መለሰና ጌት ሆይ አንድ ሚሊዮን ዶላር ስጠኝ? አለው ጌታም አንድ ሰከንድ ልጄ! አለው
ለፈገግታ
1 የጌታ ሰራዊት
የፊልድ ስራ የሚሰራ በተወሰነ ጊዜ ብቻ ወደ ከተማ የሚመጣ አንድ ጋደኛየ አንድ ቀን ከቤተክርስቲያን እየወጣ እንደ ተለመደው ሰባኪው በሩ ጋር እጅ እየጨበጠ ያሰናብት ነበረ:: የጋደኛየን እጅ ወደራሱ ሳብ አደረገና መጋቢው እንዲህ አለው < ወደ ጌታ ሰራዊት ልትቀላቀል ይገባሃል!> ጋደኛየም መለሰና <የጌታን ሰራዊት ከተቀላቀልኩ እኮ ቆይቻለሁ> አለ መጋቢውም መለስ አድርጎ <ታዲያ ለምን ድነው ከገናና ከፋሲካ በአላት በቀር ያማላይህ?> ጋደኛየም ተጫዋች ኖሮ ወደ ጆሮው ጠጋ አለና <በደህንነት ክፍለ ሰራዊት ውስጥ ስለተመደብኩ የስውር ወታደር ነኝ > አለው
2 የሞተው ቤተ/ክ
በአንድ ትንሽ ከተማ አንድ አዲስ መጋቢ የመጀመርያ አራት ቀናቶች የቤተ/ክ ምእመኖችን እየጎበኘ አሳለፈ በእሁዱ የመጀመርያ አገልግሎቱ ማንም አልመጣም በዚህም ምክንያት አገልጋዩ በከተማው ጋዜጣ ቤተ/ክኒቱ ስለሞተች ከቀብር ስነስርአቱ በፊት አስክሬኑን መሰናበት የእየአንዳዱ ምእመን ግዴታ ነው: ሽኝቱም በዚህ ቦታ ነው ብሎ ሰአቱን አስታወቀ::
ብዙ ምእመኖችም በመደነቅ ሁኔታውን ለማየት ግልብጥ ብለው ወጡ: በፑልፒቱ ስርም የሬሳ ሳጥን ከአበባ ጋር ተጋድሞ አዩ ሰባኪው
ንግግሩን ከጨረሰ ቡሁላ ኮፈኑን ከፍቶ የሞተችውን ቸርች አስክሬን ወደፊት መጥተው ተገቢውን የመሰናበቻ አክብሮት እንዲሰጡ ጋበዘ: : ሁሉም በድኑን ወክሎ የተቀመጠው ምን ይሆን ብለው በችኮላ ወደ ተከፈተው ኮፈን እየተንጠራሩ ሲመለከቱ ሰውየው ብልህ ኖሮ ያስቀመጠው ከጥግ እስከ ጥግ ትልቅ የፊት ማሳያ መስተዋት ነበረ ሁሉም የመለካቸውን ነጸብራቅ አይተው ተኮነኑ::
3 ከተማው ተወረዋልና
አንድ ሰባኪ በአንድ ከተማ ኮንፍረንስ ሊያገለግል ተጋበዘ በአገልግሎቱ መጨረሻ ክፉ ላደረበት ሰው ይፈወስ ዘንድ መፀለይ ጀመረ በስሙ ስልጣን አጋንንትን ከማስወጣቱ በፊትም ኢንተርቪው ወይም ቃለ መጠየቁን ጀመረ ስምህ ማነው? አለው ንፁሁ ያልሆነውም መንፈስም ቃል ጠቅሶ ብዙ ነንና ጌልዮን! ብሎ መለሰለት ሰባኪውም ደግሞ ስንት ናችሁ? ብሎ ጥያቄውን ደገመ እርኩስ መንፈሱም 10ሺ ነን! አለው ሰባኪውም በመደነቅ ደንገጥ አለና የውሸት አባት መሆኑን ዘንግቶት ኖሮ የሰማውን ስላመነው ወደ ሰዎቹ ዘወር አለና ከተማው ተወረዋልና የ3ቀን ጾም ጸሎት ይታወጅ! አለ::